You are here: HomeSocial Issues Videoአንጡራ ክርስትና - Introduction

አንጡራ ክርስትና - Introduction

Published in Video Friday, 17 July 2015 06:59

በዚህ ባለንበት ዘመን በሐገራችን የወንጌላውያን ክርስትና የአደባባይ ገጽታ የተሟላ ነው ለማለት አያስደፍርም፡፡ ለዚህ ዋነኛው ማስረጃ የወንጌሊውያን ክርስትና በዋነኛነት እየተወከለ የሚገኘው አምልኮ፣ ፈውስ፣ ጸሎት፣ ትንቢት በመሳሰለት ነገሮች ብቻ ነው፡፡ እነዚህ ነገሮች እጅግ በጣም አስፈላጊና መሠረታዊ ናቸው ፡፡ ቢሆንም ግን የወንጌላውያን ክርስትና አማኝ ተኮር ፣ ልብ- ተኮር እንጂ አመለካከት እና ዓለም- ተኮር ሲሆን አይታይም፡፡

 

ከዚህም የተነሳ በርካታ ችግሮች ተከስተዋል፡፡ ከእነዚህም መካከል ጥቂቶቹ የሚከተለት ናቸው፡-

 

1. አማኞች ስለ መጽሐፍ ቅደስ ያላቸው ዕውቀት ሲታይ አናሳ የሚባል ደረጃ ላይ የሚገኝ ነው፡፡

2. አማኞች ከመናፍቃን የሚነሱባቸው እምነትን የሚነቀንቁ ጥያቄዎች ምላሽ መስጠት ተስኗቸው አንገታቸውን ሲደፉ ይታያሉ፡፡

3. አማኞች በሐገራችን ሰፊ ስፍራ በሚሰጣቸው ጉዳዮች ላይ ያላቸው ተሰሚነት አናሳ ነው፡፡

4. ከላይ ከዘረዘርናቸው ችግሮች የተነሳ አማኞች ወንጌልን ለመኖር እና ለመመስከር ያላቸው ድፍረት እየደበዘዘ መጥቷል፡፡

 

እነዚህ ከላይ የዘርረዘርናቸው ችግሮች መፍትሄ ተደርጎ ሊታይ የሚገባው ዘመን ባፈራው መንገድ አማኞች ክርስቲያናዊ አመለካከት እንዲያዳብሩ እና ክርስቲያናዊ ሕይወትን እንዱኖሩ ከዚህም የተነሳ ደግሞ ስለ ጌታ የማያምኑ ሰዎች በድፍረት መመስከራቸው ነው፡፡ ይህን ለማምጣት የሚረዳን የሚዲያውን አድማጭ-ተመልካች በሚመጥን መልኩ የተዘጋጀ ተከታታይ እና ጥልቅ ትምህርት ነው፡፡

Read 9640 times Last modified on Monday, 20 July 2015 07:26
Abinet Ababu

I am Abinet Ababu a disciple, a husband and a father of two. A graduate of for Evangelical Theological college (ETC) in Bible Translation and Literacy. A student at at Africa Nazarene University (Nairobi, Kenya). A Bible school teacher, speaker and writer. An Interpreter by trade (to Amharic,English to Ormiffa -pending). 

Website: abinetababu.wordpress.com Email This email address is being protected from spambots. You need JavaScript enabled to view it.

Nahu's Corner

 

 

 

.

Right Now

We have 138 guests and no members online

About Us

Semayawi Thought is an online magazine published in Amharic and English, focused on contents to spiritual and personal growth.