ዶ/ር በቀለ ብርሃኑ በ1990 ዓ.ም ከአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ሜዲካል ፋኩልቲ በኤም.ዲ ተመርቀዋል፡፡በተጨማሪም ቤልጂየም ውስጥ በሚገኝ አንድ ዩኒቨርሲቲ ለዐሥር ወራት የስትራቴጂክ ማኔጅመንት ኦፍ ሄልዝ ሰርቪስስ (strategic management of health services) ሥልጠና ተከታትለዋል፡፡ በአሁኑ ወቅት አሜሪካ ጌትስበርግ በመኖሪያቸው አቅራቢያ በሚገኝ አንድ ሆስፒታል በሳምንት ሦስት ቀን ይሠራሉ፡፡ጌታን እያገለገሉ ከባለቤታቸው ከወይዘሮ አባይና ከሦስት ልጆቻቸው ጋር በአሜሪካን አገር በመኖር ላይ ይገኛሉ፡፡በ2014 አመተ ምሕረት የራሳቸውን ግለ-ታሪክ ጽፈዋል፡፡፡፡ርእሱም ከጨለማ ወደ ሚደነቅ ብርሃን የሚል ሲሆን በኢትዮጵያና በእዚህ በአገረ አሜሪካ በተለያዩ ቦታዎች እየተሸጠ ይገኛል፡፡እንዲሁም በዚህ በ2015 ዓ.ም ገጣሚው በሚል ርእስ የግጥም መድብል ለሕዝብ ንባብ አበርክተዋል፡፡በተጨማሪም በተለያዩ ድረ-ገጾችና ሶሻል ሜድያዎች የተለያዩ መጣጥፎችንና ግጥሞች በማበርከት ላይ ይገኛሉ፡፡
.