You are here: HomeNews/Eventsየአሜሪካ ጠቅላይ ፍርድ ቤት ታሪካዊ ውሳኔ

የአሜሪካ ጠቅላይ ፍርድ ቤት ታሪካዊ ውሳኔ

Written by  Published in News and Events Friday, 26 June 2015 00:00

የአሜሪካ ጠቅላይ ፍርድ ቤት ዛሬ ላይ በዋለው ችሎት ታሪካዊ የሆነ ውሳኔ አስተላልፏል፡፡ ፍርድ ቤቱ የተመሳሳይ ጾታ ጋብቻ በሁሉም 50 ስቴቶች ህጋዊ መሆኑን ደንግጓል፡፡

 

በቅድሚያ 3 ስቴቶች ብቻ ይፈቅዱት የነበረው የተመሳሳይ ጾታ ጋብቻ ወደ 37 ስቴቶች አድጎ የቆየ ሲሆን ጠቅላይ ፍርድ ቤቱ ግብረ ሰዶማዊነትን ጠቅልሎ ህጋዊ ተግባርና የሁሉም ዜጎች መብት እንደሆነ ወስኗል፡፡

 

ፍርድ ቤቱ ጋብቻ ምን እንደሆነ ገለጻም ሆነ ትርጉም አልሰጠም፡፡ እንዲው በደፈናው ከተመሳሳ ጾታ ጋር ጋብቻ መፈጸም እንደሚቻልና የሁሉም አሜሪካዊ ዜጋ መብት እንደሆነ ውሳኔውን አስተላልፏል፡፡

 

የፍርድቤቱን የመጨረሻ ውሳኔ በመጠበቅ ላይ የነበሩ በርካታ ሰዎች የፍርድቤቱን አካባቢ በጩኸትና በፌሽታ አድምቀውታል፡፡ በአንጻሩ ደግሞ ሌሎች በርካቶች ተቃውሞአቸውን በተለያየ መንገድ በመግለጽ ላይ ናቸው፡፡

 

የአሜሪካ መንግስትና ሌሎች በሥልጣኔ ጫፍ ወጥተዋል የምንላቸው ምዕራባዊ ሀገራት ነገረ ሥራ ሁሉ ጥንት መንግስታቶቻቸውና ሕዝቦቻቸው የቆሙለትን ሞራላዊና ኃይማኖታዊ እሴቶችን በመናድ (እነሱ በፈረንጅኛቸው እንደሚሉት - re-define) ማድረጉን ተያይዘውታል፡፡

 

በአሜሪካ የተደረገው ማንኛውም ነገር በቀረው ዓለም የሚኮረጅ እንደመሆኑ ወይም በተለያዩ የዲፕሎማሲ መሥመሮች በዕርዳታና በብድር ውዴታ ግዴታ መንገዶች ነገ በእኛ ላይም መጫኑ ስለማይቀር ነቅተን ምድራችንን በጸሎት ልንናጠቅ ይገባል፡፡

 

ጋብቻ የአሜሪካ መንግስት ከመፈጠሩም በፊት የነበረና ሰዎችን ወንድና ሴት አድርጎ በፈጠረው በእግዚአብሔር አምላክ በራሱ የተፈጠረ ተቋም ነው፡፡ ወንድና ሴት አድርጎ የፈጠራቸው እግዚአብሔር በሥራው ትክክልና የማንንም ማስተካከያ አይሻም፡፡

 

ወሬው ሁሉ፣ የሚሰማው ሁሉ አስፈሪና የጌታን ዳግም ምጽአት የሚያመላክት በመሆኑ ነቅተን ዘመኑን ልንዋጅ ይገባል፡፡

Read 6907 times Last modified on Saturday, 27 June 2015 05:05
Mesay Matusala

Mesay Matusala is a single (unmarried) man and a member of Hawassa Tabor Mekane Yesus congregations in Hawassa. He is a business and development professional, working employed for the last 7 years. Currently is focusing on writing, translation, and preparing to start a company in children and youth development and entertainment.

Email This email address is being protected from spambots. You need JavaScript enabled to view it.

Nahu's Corner

 

 

 

.

Right Now

We have 299 guests and no members online

About Us

Semayawi Thought is an online magazine published in Amharic and English, focused on contents to spiritual and personal growth.