You are here: HomeNews/Eventsየአዲስ አበባ ክልል መሠረተክርስቶስ ቤተክርስቲያን የመዘምራን አገልግሎት የተመሠረተበት የ40ኛ ዓመት በዓል ተከበረ

የአዲስ አበባ ክልል መሠረተክርስቶስ ቤተክርስቲያን የመዘምራን አገልግሎት የተመሠረተበት የ40ኛ ዓመት በዓል ተከበረ

Published in News and Events Monday, 09 June 2014 00:00

የአዲስ አበባ ክልል መረተክርስቶስ ቤተክርስቲያን የመዘምራን አገልግሎት የተመሠረተበትን  የ40ኛ ዓመት በዓል ከትላንት በስቲያ ግንቦት 30 እና በትላንትናው ለት ሰኔ 1 ቀን 2006 ዓ.ም. በደማቅ ሁኔታ በምስራቅ መረተ ክርስቶስ ቤተክርስቲያን ተከብሮ ውል። 

 

የኢትዮጵያ ወንጌላውያን አብያተ ክርስቲያናት ኀብረት ዋና ፀሐፊ ቄስ  ዓለሙ ሼጣ የእንኳን አደረሳችሁ መልእታቸውን በማስተላለፍ ፕሮግራሙን የከፈቱ ሲሆን ፥በእነዚህ ዓርባ ዓመታት መዘምራኑ ከራሳቸው ቤተ እምነት አልፈው ለመላው ወንጌላውያን አማኞች በረከት የሆኑበትን መንገድ በማስታወስ ፥ ወንጌላውያን አማኞች ባለፉበት የስደት እና የመከራ ጊዜያት ሁሉ የፅናትና የማበረታቻ ዝማሬዎችንና ዓውድን የጠበቁ መልዕክቶችን ለልባችን በማድረስ ባርከውናል ብለዋል።

 

አቶ ቴዎድሮስ በየነ የመሠረተ ክርስቶስ ቤተክርስቲያን ሊቀመንበርም ፥ "ይህ የመዘምራን ቡድን ይህን ምስክርነት ሳይለቅ የሚተኩ ትውልዶችን እየተቀባበለ እስከ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ዳግም ምጽአት እንዲቀጥል ጸሎቴ ምኞቴም ነው" ብለዋል።

 

የመዘምራኑ መሪ አቶ ሰለሞን ደምሴ ፥ የአዲስ አበባ ክልል መዘምራን የተመሠረተበትን 40ኛ ዓመት በዓልን ለማክበርና በዘመናት ሁሉ የረዳቸውን እግዚአብሔርን ለማመስገን ታስቦ የተዘጋጀ ፕሮግራም መሆኑን ጠቅሰው የመዘምራኑን የ40 ዓመታት አገልግሎት ታሪክ በአጭሩ ለታዳሚው አቅርበዋል።

 

በመዘምራኑ እስከዛሬ የተዘመሩ መዝሙሮችን በድህረገጽ በነጻ መለለቀቃቸውንና ፥ማንም ሰው online ማድመጥ ፥ download ማድረግና social network ድህረገጾች ላይ share ማድረግ እንደሚችል ፥ የድህረገጹም አድራሻ www.mkchoir.org እንደሆነ ገልጸዋል።

 

በእነዚህ ሁለት ቀናትም የተለያዩ ዝግጅቶች የቀረቡ ሲሆን ፥ ከዝግጅቶቹም መሃል የአጥቢያዎች ዓውድርይና ለዚህ በዓል ብለው ከባህር ማዶ የመጡ የመዘምራኑ አባላት ምስክርነት ይገኙበታል።

 

Semayaiw Thought በዚህ አጋጣሚ ለመዘምራኑ የእንኳን አደረሳችሁ መልእክቱን እያስተላለፈ እግዚአብሔር ቀጣይ አገልግሎታችሁን ይባርክ ይላል።

 

Read 5855 times Last modified on Monday, 09 June 2014 18:16

Nahu's Corner

 

 

 

.

Right Now

We have 21 guests and no members online

About Us

Semayawi Thought is an online magazine published in Amharic and English, focused on contents to spiritual and personal growth.