በዘመናችን በአብዛኛው ሰው የእጅ ሰአት፣ ተንቀሳቃሽ ስልክና የመሳሰሉትን ጊዜ ጠቋሚ መሣሪያዎች ይጠቀማል፡፡ በእለታዊ እንቅስቃሴያችን አዘውትረን የምንሰማቸው እንደ “ጊዜ የለኝም፣ ጊዜህን አታባክን፣ ጊዜያችንን በአግባቡ እንጠቀም” የመሳሰሉ አባባሎች ሰዎችና ጊዜ ቢያንስ በዚህ ምድር ላይፋቱ መቆራኘታቸውን ያሳዩናል፡፡ እንደነዚህ ያሉ ሐረጋት በየንግግሮቻችን መኻል ቢደመጡም በአገራችን ለጊዜ የሰጠነው ዋጋ አነስተኛ ለመሆኑ “ጥናት ላይ የተመሰረተ መረጃ ካልቀረበልኝ አላምንም” የሚያሰኝ አይደለም፤ ይልቁን ለሁሉ ግልጥ ሆኖ የሚታይ ነው፡፡ ከዚህም የተነሳ የ...