ጥርቅምቃሞ ተስፋው ነጥፎ
ከነፍሱ ጭላጭ ተንጠፍጥፎ
ሲነጋ ሲመሽ ተጋድሞ
ስጋው የልቡም ለብ ታሞ
እንዳይሞት ብቻ ኖሮ
በሁለትዮሽ ትብታብ
ታብቶ በመከራ ጥላ ድባብ
ላይቀና ከጋድሚያው ነቅቶ
ላይረግፍ ላያልፍ እሱ ሞቶ
ተራውን በግድ ተቀምቶ
ላይሆንለት ማቅቆ ማቆ
ሰው አጣሁኝ ቅኔውን
የብቻነት በገናውን
አንዝሮ ሰብቆ ክብሩን
አፏጭቶ ተንፍሶ መቃወን
የምሬት እንጉረጉሮ ዜማ
ቀንና ለሊት ሲያሰማ
ያለ ልቅሶ ስራ ቢያጣ
ፀሀይ ጠልቆ እሰኪወጣ
ንጋት ወዲህ እሰኪያገኘው
ሰው የለኝም የሱ ቅኔው
ውሃው ወዲያ ወዲህ ሲሰፍ
በመላዕክት እጅ...