ጥር 16 ቀን 2003 ዓ.ም ከምሽቱ አምስት ሰዓት በኋላ ነው፡፡ ቢ.ጂ.ኤም በሚባል የማዋለጃ ሆስፒታል ውስጥ ባለቤቴ የመጀመሪያ ልጃችንን ለመውለድ ማዋለጃ ክፍል ውስጥ ተኝታ የምጥ ጣር ይዟት ትጮኻለች፡፡
እኔም በሀገራችን ሚስት ስትወልድ በማዋለጃ ክፍል መገኘት ያልተለመደ ስለሆነ (ከኮሪያ ሆስፒታል በስተቀር) እያማጠች ያለችበት ክፍል መስኮት አጠገብ ቆሜ ከውስጥ የሚወጡ ድምፆችን ጆሮዬን ተክዬ አዳምጣለሁ፡፡ ወዲያውም ደግሞ ወደ እግዚአብሔር ልመናዬን አቀርባለሁ፡፡ በህይወቴ እንደዛች ቀን ተጨንቄ የማውቅ አይመስለኝም፡፡ ባለቤቴን እንደምወዳት በት...