በተለያዩ የአምልኮ ስፍራዎች ተገኝታችሁም ሆነ (ቴክኖሎጂ ይመስገንና) በማህበራዊ ድረ-ገጾች ጭምር የአምልኮ ፕሮግራሞችን ተከታትላችሁ የራሳችሁን አስተያየት (ጥሩም ይሁን መጥፎ) በልባችሁ አስተያየት መስጫ ስር አስቀምጣችሁ ታውቁ ይሆናል፡፡ ከአንድ ዓመት በፊት በተመሳሳይ ጉዳይ ላይ ያነሳሁት አንድ ጥያቄ ተመልሶ ስለመጣብኝ ዛሬ ላወራው ተገድጃለሁ፡፡ አምልኮአችን እግዚአብሄርን እያስደሰተው ነው ወይስ እኛን እያዝናናን ነው? የእግዚአብሄር ህዝብ ረሃብስ ቃሉን ነው ወይስ መዝናናትን? ከዚህ ጥያቄ ትኩሳት ውስጥ ሳንወጣ ሌላ ጥያቄ፤ እግዚአብሄርን እያመለክን...