መቼም መዘመር መልካም ነው ለጌታ የሚገባውን ማቅረብ ይገባናል መጽሐፍ ቅዱሳዊም ነው። ግን ግን አንዳንዴ ጥያቄ እንድጠይቅ የሚያደርጉኝ፡ ነገሮች አሉ እንደው እንዳላየ ሆኜ ለማለፍ ካልፈለኩ በቀር፡ አምልኮ ጭፈራችን ነው ወይንስ ሕይወታችን? አካሄዳችን ወዴት ነው? ምን እያደረግን ነው? በእኛና በዚያኛው (በዓለማዊው) ሰፈር ያለው ልዩነት ምን መሆን አለበት?
የመገናኛ ብዙኃን (Social network) በሰፊው ግልጋሎት ላይ ከዋለ ጊዜ ጀምሮ እየጨመረ እያደጉ ያሉ ብዙ ጠቃሚ አስተማሪና ግንዛቤ ሰጪ ነገሮች ማግኘት ችለናል። ይሄ እውነት ሆኖ እ...