ከተለያዩ ድርጅቶችና ሚኒስትሪዎች እንዲሁም 17 ከሚሆኑ የተለያዩ የአፍሪካና ሌሎች አህጉራት የተወጣጡ ሰዎች የተሳተፉበት Inigitous Addis የተሰኘ ኮንፈረንስ ተካሄደ:: በዲጂታል ስልት ክርስቶስን በአንድ ልብ የማካፈል ጥማት ያላቸው ሰዎች የተሳተፉበት ሲሆን ፥ በዚህም ኮንፈረንስ ወቅት የተለያዩ የቤተክርስቲያን መሪዎችና አጋር ድርጅቶች Indigitous Initiativeን እንደሚደግፉና እንደሚያበረታቱ ገልፀዋል፡፡
ይህ ኮንፈረንስ በአዲስ አበባ ሂልተን ሆቴል የተዘጋጀው ከሚያዝያ 30 - ግንቦት 2፥ 2006 ዓ.ም. ለ 3 ቀን ሲሆን ፥ በ በኮንፈረንሱ የተገኙ ተሳታፊዎች ዲጂታል ሚዲያን ባማከለ ፕሮግራም ላይ በመገኘታቸው ደስታቸውን ገልጸዋል።